Asset Publisher

null አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ ሌሎች ታዋቂ ግለሰቦች የታክስ እና የጉምሩክ አምባሳደሮች ሆነው ተሰየሙ

አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ ሌሎች ታዋቂ ግለሰቦች የታክስ እና የጉምሩክ አምባሳደሮች ሆነው የተሾሙ ሲሆን ከ2011 ጀምሮ በታክስ አምባሳደርነት ሲያገለግሉ የነበሩ ግለሰቦችም የክብር ሽኝት ተደርጎላቸዋል፡፡

አዲስ የተሾሙት አምባሳደሮች የሀገርን ገጽታ በመገንባት፣ የማህበረሰብን አስተሳሰብ በበጎ በመቅረጽ እና ማህበራዊ ኃላፊነቶቻቸውን በመወጣት በኩል  ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ  ናቸው፡፡

የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፣ በክብር የተሸኙትን አመስግነው አዲስ የተሾሙት የታክስ አምባሰደሮች የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ  ጠይቀዋል፡፡

አዲስ የተሰየሙ የታክስ አምባሳደሮች
1.  አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ
2.  አቶ ግርማ ገ/ጻድቅ
3.  ሊቀ ትጉኃን ታጋይ ታደለ
4.  አቶ ቢኒያም በለጠ
5.  ወ/ሮ ሀናን መሀመድ
6.  ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ
7.  ዶ/ር ማሙሽ ፈንታ
8.  ዶ/ር ወዳጀነህ ማሀረነ
9.  ዶ/ር ምህረት ደበበ

በክብር የተሸኙ የታክስ አምባሳደሮች
1.  ደራሲ ጌታቸው በለጠ
2.  አርቲስት አረጋኻኝ ወራሽ
3.  አርቲስት ሀመልማል አባተ
4.  መጋቢ ኃዲስ እሸቱ አለማየሁ
5.  ሙኃዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
6.  ኡስታዝ አቡበከር አህመድ
7.  አምባሰደር ሀሰን ታጁ
8.  አትሌት ጡሩነሽ ዲባባ
9.  ሎሬት የትነበርሽ ንጉሴ
10.  አምባሰደር ሙሉ ሰሎሞን

የጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaCustomsCommission

Asset Publisher